Constitution of the Federal Democratic Republic of Ethiopia 1994
Affirmative Action (Broadly)
  • English

    3. The historical legacy of inequality and discrimination suffered by women in Ethiopia taken into account, women, in order to remedy this legacy, are entitled to affirmative measures. The purpose of such measures shall be to provide special attention to women so as to enable them to compete and participate on the basis of equality with men in political, social and economic life as well as in public and private institutions.
    … (Art. 35)
  • Amharic

    3. ሴቶች በበታችነትና በልዩነት በመታየታቸው የደረሰባቸውን የታሪክ ቅርስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህ ቅርስ እንዲታረምላቸው በተጨማሪ የድጋፍ እርምጃዎች ተጠቃሚ የመሆን መብት አላቸው፡፡ በዚህ በኩል የሚወሰዱት እርምጃዎች ዓላማ በፖለቲካዊ፣ በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ መስኮች እንዲሁም በመንግሥት እና በግል ተቋሞች ውስጥ ሴቶች ከወንዶች ጋር በእኩልነት ተወዳዳሪና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ እንዲቻል ልዩ ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡
    … (አንቀጽ 35)
Citizenship and Nationality
  • English
    1. Any person of either sex shall be an Ethiopian national where both or either parent is Ethiopian.
    2. Foreign nationals may acquire Ethiopian nationality.
    3. Particulars relating to nationality shall be determined by law. (Art. 6)
  • Amharic
    1. ወላጆቹ/ወላጆቿ ወይም ከወላጆቹ/ከወላጆቿ አንደኛቸው ኢትዮጵያዊ/ኢትዮጵያዊት የሆነ/የሆነች የኢትዮጵያ ዜጋ ነው/ናት፡፡
    2. የውጭ ሀገር ዜጐች የኢትዮጵያ ዜግነት ሊያገኙ ይችላሉ፡፡
    3. ዜግነትን በሚመለከት ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፡፡ (አንቀጽ 6)
Citizenship and Nationality
  • English
    1. No Ethiopian national shall be deprived of his or her Ethiopian nationality against his or her will. Marriage of an Ethiopian national of either sex to a foreign national shall not annul his or her Ethiopian nationality.
    2. Every Ethiopian national has the right to the enjoyment of all rights, protection and benefits derived from Ethiopian nationality as prescribed by law.
    3. Any national has the right to change his Ethiopian nationality.
    4. Ethiopian nationality may be conferred upon foreigners in accordance with law enacted and procedures established consistent with international agreements ratified by Ethiopia. (Art. 33)
  • Amharic
    1. ማንኛውም ኢትዮጵያዊ/ኢትዮጵያዊት ከፈቃዱ/ከፈቃዷ ውጭ ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን/ዜግነትዋን ሊገፈፍ ወይም ልትገፈፍ አይችልም/አትችልም፡፡ ኢትዮጵያዊ / ኢትዮጵያዊት ዜጋ ከሌላ ሀገር ዜጋ ጋር የሚፈጽመው/የምጽትፈጽመው ጋብቻ ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን / ዜግነትዋን አያስቀርም፡፡
    2. ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ የኢትዮጵያ ዜግነት በሕግ የሚያስገኘውን መብት ጥበቃና ጥቅም የማግኘት መብት አለው፡፡
    3. ማንኛውም ዜጋ ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን የመለወጥ መብት አለው፡፡
    4. ኢትዮጵያ ከአጸደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ጋር በማይቃረን መንገድ በሚወጣ ሕግ እና በሚደነገግ ሥርዓት መሰረት የኢትዮጵያ ዜግነት ለውጭ ሀገር ሰዎች ሊሰጥ ይችላል፡፡ (አንቀጽ 33)
Citizenship and Nationality
  • English

    1. The House of Peoples' Representatives shall have the power of legislation in all matters assigned by this Constitution to Federal jurisdiction.
    2. Consistent with the provision of sub-Article 1 of this Article, the House of Peoples' Representatives shall enact specific laws on the following matters:

    e. Nationality,
    … (Art. 55)

  • Amharic

    1. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት ለፌዴራሉ መንግሥት በተሰጠው የሥልጣን ክልል ሕጐችን ያወጣል፡፡
    2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 የተመለከተው አጠቃላይ ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ዝርዝር ሕግ ያወጣል፤

    ሠ/ የዜግነት መብትን፤
    … (አንቀጽ 55)

Jurisdiction and Access
  • English
    1. The House has the power to interpret the Constitution.
    … (Art. 62)
  • Amharic
    1. ምክር ቤቱ ሕገ መንግሥቱን የመተርጐም ሥልጣን ይኖረዋል፡፡
    … (አንቀጽ 62)
Jurisdiction and Access
  • English
    1. All constitutional disputes shall be decided by the House of the Federation.
    2. The House of the Federation shall, within thirty days of receipt, decide a constitutional dispute submitted to it by the Council of Constitutional Inquiry. (Art. 83)
  • Amharic
    1. የሕገ መንግሥታዊ ክርክር ጉዳይ ሲነሳ በፌዴሬሽኑ ምክር ቤት ውሳኔ ያገኛል፡፡2. የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ በሚያቀርብለት ሕገ መንግሥታዊ ጉዳይ ላይ በሠላሣ ቀናት ውስጥ ውሳኔ ይሰጣል፡፡ (አንቀጽ 83)
Jurisdiction and Access
  • English

    1. The Council of Constitutional Inquiry shall have powers to investigate constitutional disputes. Should the Council, upon consideration of the matter, find it necessary to interpret the Constitution, it shall submit its recommendations thereon to the House of the Federation.
    2. Where any Federal or State law is contested as being unconstitutional and such a dispute is submitted to it by any court or interested party, the Council shall consider the matter and submit it to the House of the Federation for a final decision.
    3. When issues of constitutional interpretation arise in the courts, the Council shall:
    a. Remand the case to the concerned court if it finds there is no need for constitutional interpretation; the interested party, if dissatisfied with the decision of the Council, may appeal to the House of the Federation.
    b. Submit its recommendations to the House of the Federation for a final decision if it believes there is a need for constitutional interpretation.
    … (Art. 84)

  • Amharic

    1. የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮችን የማጣራት ሥልጣን ይኖረዋል፡፡ በሚያደርገው ማጣራት መሰረት ሕገ መንግሥቱ መተርጐም አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ለፌዴሬሽን ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ የውሳኔ ሐሳብ ያቀርባል፡፡
    2. በፌዴራሉ መንግሥትም ሆነ በክልል ሕግ አውጪ አካላት የሚወጡ ሕጐች ከዚህ ሕገ መንግሥት ጋር ይቃረናሉ የሚል ጥያቄ ሲነሳና ጉዳዩም በሚመለከተው ፍርድ ቤት ወይም በባለ ጉዳዩ ሲቀርብለት መርምሮ ለመጨረሻ ውሳኔ ለፌዴሬሽኑ ምክር ቤት ያቀርባል፡፡
    3. በፍርድ ቤቶች የሕገ መንግሥት ትርጉም ጥያቄ ሲነሳ፣
    ሀ/ ሕገ መንግሥቱን መተርጐም አስፈላጊ ሆኖ ሳያገኘው ሲቀር ጉዳዩን ለሚመለከተው ፍርድ ቤት ይመልሳል፤ በአጣሪ ጉባኤው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ባለጉዳይ ቅሬታውን ለፌዴሬሽኑ ምክር ቤት በይግባኝ ማቅረብ ይችላል፡፡
    ለ/ የትርጉም ጥያቄ መኖሩን ያመነበት እንደሆነ በጉዳዩ ላይ የሚሰጠውን ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ለፌዴሬሽኑ ምክር ቤት ለመጨረሻ ውሳኔ ያቀርባል፡፡
    … (አንቀጽ 84)

Education
  • English
    1. To the extent the country's resources permit, policies shall aim to provide all Ethiopians access to … education, …
    2. Education shall be provided in a manner that is free from any religious influence, political partisanship or cultural prejudices. (Art. 90)
  • Amharic
    1. የሀየሀገሪቱ አቅም በፈቀደ መጠን ሁሉም ኢትዮጵያዊ የትምህርት፣ … እንዲኖረው ይደረጋል፡፡
    2. ትምህርት በማናቸውም ረገድ ከሃይማኖት፣ ከፖለቲካ አመለካከቶች እና ከባህላዊ ተፅእኖዎች ነጻ በሆነ መንገድ መካሔድ አለበት፡፡ (አንቀጽ 90)
Employment Rights and Protection
  • English

    5. a. Women have the right to maternity leave with full pay. The duration of maternity leave shall be determined by law taking into account the nature of the work, the health of the mother and the well-being of the child and family.
    b. Maternity leave may, in accordance with the provisions of law, include prenatal leave with full pay.

    8. Women shall have a right to equality in employment, promotion, pay, and the transfer of pension entitlements.
    … (Art. 35)
  • Amharic

    5. ሀ/ ሴቶች የወሊድ ፈቃድ ከሙሉ የደመወዝ ክፍያ ጋር የማግኘት መብት አላቸው፡፡ የወሊድ ፈቃድ ርዝመት ሴቷ የምትሠራውን ሥራ ሁኔታ፣የሴቷን ጤንነት፣ የሕጻኑንና የቤተሰቡን ደህንነት ከግምት ውስጥ በማስገባት በሕግ ይወሰናል፡፡
    ለ/ የወሊድ ፈቃድ በሕግ በሚወሰነው መሰረት ከሙሉ የደመወዝ ክፍያ ጋር የሚሰጥ የእርግዝና ፈቃድን ሊጨምር ይችላል፡፡

    8. ሴቶች የቅጥር፣ የሥራ እድገት፣ የእኩል ክፍያና ጡረታን የማስተላለፍ እኩል መብት አላቸው፡፡
    … (አንቀጽ 35)
Employment Rights and Protection
  • English
    1. Every Ethiopian has the right to engage freely in economic activity and to pursue a livelihood of his choice anywhere within the national territory.
    2. Every Ethiopian has the right to choose his or her means of livelihood, occupation and profession.

    7. The State shall undertake all measures necessary to increase opportunities for citizens to find gainful employment.
    … (Art. 41)
  • Amharic
    1. ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በሀገሪቱ ውስጥ በማንኛውም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመሰማራትና ለመተዳደሪያው የመረጠውን ሥራ የመሥራት መብት አለው፡፡
    2. ሁሉም ኢትዮጵያዊ መተዳደሪያውን፣ ሥራውንና ሙያውን የመምረጥ መብት አለው፡፡

    7. መንግሥት ዜጐች ጠቃሚ ሥራ የማግኘት ዕድላቸው እየሰፋ እንዲሄድ ለማድረግ አስፈላጊ እርምጃዎችን ይወስዳል፡፡
    … (አንቀጽ 41)
Employment Rights and Protection
  • English

    d. Women workers have the right to equal pay for equal work.
    2. Workers have the right to reasonable limitation of working hours, to rest, to leisure, to periodic leaves with pay, to remuneration for public holidays as well as healthy and safe work environment.
    … (Art. 42)
  • Amharic

    መ/ሴቶች ሠራተኞች ለተመሳሳይ ሥራ ተመሳሳይ ክፍያ የማግኘት መብታቸው የተጠበቀ ነው፡፡
    2. ሠራተኞች በአግባቡ የተወሰነ የሥራ ሰዓት ዕረፍት፣ የመዝናኛ ጊዜ፣ በየጊዜው ከክፍያ ጋር የሚሰጡ የዕረፍት ቀኖች፣ ደመወዝ የሚከፈልባቸው የሕዝብ በዓላት እንዲሁም ጤናማና አደጋ የማያደረስ የሥራ አካባቢ የማግኘት መብት አላቸው፡፡
    … (አንቀጽ 42)
Equality and Non-Discrimination
  • English
    We, the Nations, Nationalities and Peoples of Ethiopia: …
    Firmly convinced that the fulfillment of this objective requires full respect of individual and people’s fundamental freedoms and rights, to live together on the basis of equality and without any sexual, religious or cultural discrimination;
    … (Preamble)
  • Amharic
    እኛ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ …
    ይህን ዓላማ ከግብ ለማድረስ፣ የግለሰብና የብሔር/ብሔረሰብ መሰረታዊ መብቶች መከበራቸው፣ የጾታ እኩልነት መረጋገጡ፣ ባሕሎችና ሃይማኖቶች ካለአንዳች ልዩነት እንዲራመዱ የማድረጉ አስፈላጊነት ጽኑ እምነታችን በመሆኑ
    … (መግቢያ)
Equality and Non-Discrimination
  • English
    Provisions of this Constitution set out in the masculine gender shall also apply to the feminine gender. (Art. 7)
  • Amharic
    በዚህ ሕገ መንግሥት ውስጥ በወንድ ፆታ የተደነገገው የሴትንም ፆታ ያካትታል፡፡ (አንቀጽ 7)
Equality and Non-Discrimination
  • English
    All persons are equal before the law and are entitled without any discrimination to the equal protection of the law. In this respect, the law shall guarantee to all persons equal and effective protection without discrimination on grounds of race, nation, nationality, or other social origin, colour, sex, language, religion, political or other opinion, property, birth or other status. (Art. 25)
  • Amharic
    ሁሉም ሰዎች በሕግ ፊት እኩል ናቸው፤ በመካከላቸውም ማንኛውም ዓይነት ልዩነት ሳይደረግ በሕግ እኩል ጥበቃ ይደረግላቸዋል፡፡ በዚህ ረገድ በዘር፣በብሔር፣ ብሔረሰብ፣በቀለም፣ በጾታ፣ በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ፣ በማኅበራዊ አመጣጥ፣ በሀብት፣በትውልድ ወይም በሌላ አቋም ምክንያት ልዩነት ሳይደረግ ሰዎች ሁሉ እኩልና ተጨባጭ የሕግ ዋስትና የማግኘት መብት አላቸው፡፡ (አንቀጽ 25)
Equality and Non-Discrimination
  • English
    1. Women shall, in the enjoyment of rights and protections provided for by this Constitution, have equal right with men.

    3. The historical legacy of inequality and discrimination suffered by women in Ethiopia taken into account, women, in order to remedy this legacy, are entitled to affirmative measures. The purpose of such measures shall be to provide special attention to women so as to enable them to compete and participate on the basis of equality with men in political, social and economic life as well as in public and private institutions.
    … (Art. 35)
  • Amharic
    1. ሴቶች ይህ ሕገ መንግሥት በአረጋገጣቸው መብቶችና ጥበቃዎች በመጠቀም ረገድ ከወንዶች ጋር እኩል መብት አላቸው፡፡

    3. ሴቶች በበታችነትና በልዩነት በመታየታቸው የደረሰባቸውን የታሪክ ቅርስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህ ቅርስ እንዲታረምላቸው በተጨማሪ የድጋፍ እርምጃዎች ተጠቃሚ የመሆን መብት አላቸው፡፡ በዚህ በኩል የሚወሰዱት እርምጃዎች ዓላማ በፖለቲካዊ፣ በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ መስኮች እንዲሁም በመንግሥት እና በግል ተቋሞች ውስጥ ሴቶች ከወንዶች ጋር በእኩልነት ተወዳዳሪና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ እንዲቻል ልዩ ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡
    … (አንቀጽ 35)
Obligations of the State
  • English
    We, the Nations, Nationalities and Peoples of Ethiopia: …
    Firmly convinced that the fulfillment of this objective requires full respect of individual and people’s fundamental freedoms and rights, to live together on the basis of equality and without any sexual, religious or cultural discrimination;
    … (Preamble)
  • Amharic
    እኛ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ …
    ይህን ዓላማ ከግብ ለማድረስ፣ የግለሰብና የብሔር/ብሔረሰብ መሰረታዊ መብቶች መከበራቸው፣ የጾታ እኩልነት መረጋገጡ፣ ባሕሎችና ሃይማኖቶች ካለአንዳች ልዩነት እንዲራመዱ የማድረጉ አስፈላጊነት ጽኑ እምነታችን በመሆኑ
    … (መግቢያ)
Obligations of the State
  • English
    1. Human rights and freedoms, emanating from the nature of mankind, are inviolable and inalienable.
    2. Human and democratic rights of citizens and peoples shall be respected. (Art. 10)
  • Amharic
    1. ሰብዓዊ መብቶችና ነጻነቶች ከሰው ልጅ ተፈጥሮ የሚመነጩ፣ የማይጣሱና የማይገፈፉ ናቸው፡፡
    2. የዜጐች እና የሕዝቦች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ይከበራሉ፡፡ (አንቀጽ 10)
Obligations of the State
  • English
    1. All Federal and State legislative, executive and judicial organs at all levels shall have the responsibility and duty to respect and enforce the provisions of this Chapter3.
    2. The fundamental rights and freedoms specified in this Chapter shall be interpreted in a manner conforming to the principles of the Universal Declaration of Human Rights, International Covenants on Human Rights and international instruments adopted by Ethiopia. (Art. 13)
  • Amharic
    1. በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ የፌዴራል መንግሥትና የክልል ሕግ አውጪ፣ ሕግ አስፈጻሚ እና የዳኝነት አካሎች በዚህ ምዕራፍ የተካተቱን ድንጋጌዎች የማክበርና የማስከበር ኃላፊነትና ግዴታ አለባቸው፡፡
    2. በዚህ ምዕራፍ የተዘረዘሩት መሠረታዊ የመብቶችና የነጻነቶች ድንጋጌዎች ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕግጋት፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ስምምነቶችና ዓለም አቀፍ ሰነዶች መርሆዎች ጋር በተጣጣመ መንገድ ይተረጐማል፡፡ (አንቀጽ 13)
Obligations of the State
  • English
    1. The House of Peoples' Representatives shall have the power of legislation in all matters assigned by this Constitution to Federal jurisdiction.

    7. It shall determine the organization of national defence, public security, and a national police force. If the conduct of these forces infringes upon human rights and the nation's security, it shall carry out investigations and take necessary measures.

    16. It shall, on its own initiative, request a joint session of the House of the Federation and of the House of Peoples' Representatives to take appropriate measures when State authorities are unable to arrest violations of human rights within their jurisdiction. It shall, on the basis of the joint decision of the House, give directives to the concerned State authorities.
    … (Art. 55)
  • Amharic
    1. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት ለፌዴራሉ መንግሥት በተሰጠው ሥልጣን ክልል ሕጐችን ያወጣል፡፡

    7. የፌዴራል መንግሥት፤ የሀገርና የሕዝብ መከላከያ፤ የደህንነትና የፖሊስ ኃይል አደረጃጀት ይወስናል፡፡ በሥራ አፈጻጸም ረገድ የሚታዩ መሠረታዊ የዜጐችን ሰብዓዊ መብቶችና የሀገርን ደህንነት የሚነኩ ጉዳዮች ሲከሰቱ ያጣራል፤ አስፈላጊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ያደርጋል፡፡

    16. በማንኛውም ክልል ሰብዓዊ መብቶች ሲጣሱና ክልሉ ድርጊቱን ማቆም ሳይችል ሲቀር፤ በራሱ አነሳሽነትና ያለክልሉ ፈቃድ ተገቢው እርምጃ እንዲወሰድ ለፌዴሬሽኑ ምክር ቤትና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ ጥያቄ ያቀርባል፤ በተደረሰበት ውሳኔ መሰረት ለክልሉ ምክር ቤት መመሪያ ይሰጣል፡፡
    … (አንቀጽ 55)
Obligations of Private Parties
  • English

    2. Everyone has the right to the free development of his personality in a manner compatible with the rights of other citizens.
    … (Art. 24)
  • Amharic

    2. ማንኛውም ሰው የራሱን ስብዕና ከሌሎች ዜጐች መብቶች ጋር በተጣጣመ ሁኔታ በነጻ የማሳደግ መብት አለው፡፡
    … (አንቀጽ 24)
Judicial Protection
  • English
    1. All Federal and State legislative, executive and judicial organs at all levels shall have the responsibility and duty to respect and enforce the provisions of this Chapter4.
    2. The fundamental rights and freedoms specified in this Chapter shall be interpreted in a manner conforming to the principles of the Universal Declaration of Human Rights, International Covenants on Human Rights and international instruments adopted by Ethiopia. (Art. 13)
  • Amharic
    1. በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ የፌዴራል መንግሥትና የክልል ሕግ አውጪ፣ ሕግ አስፈጻሚ እና የዳኝነት አካሎች በዚህ ምዕራፍ የተካተቱን ድንጋጌዎች የማክበርና የማስከበር ኃላፊነትና ግዴታ አለባቸው፡፡
    2. በዚህ ምዕራፍ የተዘረዘሩት መሠረታዊ የመብቶችና የነጻነቶች ድንጋጌዎች ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕግጋት፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ስምምነቶችና ዓለም አቀፍ ሰነዶች መርሆዎች ጋር በተጣጣመ መንገድ ይተረጐማል፡፡ (አንቀጽ 13)
National Human Rights Bodies
  • English
    1. The House of Peoples' Representatives shall have the power of legislation in all matters assigned by this Constitution to Federal jurisdiction.

    14. It shall establish a Human Rights Commission and determine by law its powers and functions.
    15. It shall establish the institution of the Ombudsman, and select and appoint its members. It shall determine by law the powers and functions of the institution.
    … (Art. 55)
  • Amharic
    1. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት ለፌዴራሉ መንግሥት በተሰጠው የሥልጣን ክልል ሕጐችን ያወጣል፡፡

    14. የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ያቋቁማል፤ ሥልጣንና ተግባሩን በሕግ ይወስናል፡፡
    15. የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋምን ያቋቁማል፤ ተቋሙን የሚመሩ አባላትን ይመርጣል፤ይሰይማል፡፡ ሥልጣንና ተግባሩን በሕግ ይወስናል፡፡
    … (አንቀጽ 55)
Indigenous Peoples
  • English
    1. Every Nation, Nationality and People in Ethiopia has an unconditional right to self-determination, including the right to secession.
    2. Every Nation, Nationality and People in Ethiopia has the right to speak, to write and to develop its own language; to express, to develop and to promote its culture; and to preserve its history.
    3. Every Nation, Nationality and People in Ethiopia has the right to a full measure of self-government which includes the right to establish institutions of government in the territory that it inhabits and to equitable representation in state and Federal governments.

    5. A "Nation, Nationality or People" for the purpose of this Constitution, is a group of people who have or share a large measure of a common culture or similar customs, mutual intelligibility of language, belief in a common or related identities, a common psychological make-up, and who inhabit an identifiable, predominantly contiguous territory. (Art. 39)
  • Amharic
    1. ማንኛውም የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን እስከመገንጠል ያለው መብቱ በማናቸውም መልኩ ያለ ገደብ የተጠበቀ ነው፡፡
    2. ማንኛውም የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ በቋንቋው የመናገር፣ የመጻፍ፣ቋንቋውን የማሳደግ እና ባሕሉን የመግለጽ፣ የማዳበርና የማስፋፋት እንዲሁም ታሪኩን የመንከባከብ መብት አለው፡፡
    3. ማንኛውም የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ ራሱን የማስተዳደር ሙሉ መብት አለው፡፡ ይህ መብት ብሔሩ፣ ብሔረሰቡ፣ ሕዝቡ በሰፈረበት መልክዓ ምድር ራሱን የሚያስተዳድርበት መንግሥታዊ ተቋማት የማቋቋም እንዲሁም በክልልና በፌዴራል አስተዳደሮች ውስጥ ሚዛናዊ ውክልና የማግኘት መብትን ያጠቃልላል፡፡

    5. በዚህ ሕገ መንግሥት ውስጥ «ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ» ማለት ከዚህ ቀጥሎ የተገለጸውን ባህርይ የሚያሳይ ማኅበረሰብ ነው፡፡ ሰፋ ያለ የጋራ ጠባይ የሚያንጸባርቅ ባሕል ወይም ተመሳሳይ ልምዶች ያላቸው፣ ሊግባቡት የሚችሉበት የጋራ ቋንቋ ያላቸው፣ የጋራ ወይም የተዛመደ ሕልውና አለን ብለው የሚያምኑ፣የሥነ ልቦና አንድነት ያላቸውና በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር የሚኖሩ ናቸው፡፡ (አንቀጽ 39)
Indigenous Peoples
  • English

    5. Ethiopian pastoralists have the right to free land for grazing and cultivation as well as the right not to be displaced from their own lands. The implementation shall be specified by law.
    … (Art. 40)
  • Amharic

    5. የኢትዮጵያ ዘላኖች ለግጦሽም ሆነ ለእርሻ የሚጠቀሙበት መሬት በነጻ የማግኘት፣የመጠቀምና ከመሬታቸው ያለመፈናቀል መብት አላቸው፡፡ ዝርዝር አፈጻጸሙ በሕግ ይወሰናል፡፡
    … (አንቀጽ 40)
Indigenous Peoples
  • English

    8. Ethiopian farmers and pastoralists have the right to receive fair prices for their products, that would lead to improvement in their conditions of life and to enable them to obtain an equitable share of the national wealth commensurate with their contribution. This objective shall guide the State in the formulation of economic, social and development policies.
    … (Art. 41)
  • Amharic

    8. ገበሬዎችና ዘላን ኢትዮጵውያን በየጊዜው እየተሻሻለ የሚሄድ ኑሮ ለመኖር የሚያስችላቸውና ለምርት ካደረጉት አስተዋጽኦ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ተገቢ ዋጋ ለምርት ውጤቶቻቸው የማግኘት መብት አላቸው፡፡ መንግሥት የኢኮኖሚ፣የማኅበራዊና የልማት ፖሊሲዎችን በሚተልምበት ጊዜ በዚህ ዓላማ መመራት አለበት፡፡
    … (አንቀጽ 41)
Indigenous Peoples
  • English

    2. Members of the House shall be elected from candidates in each electoral district by a plurality of the votes cast. Provisions shall be made by law for special representation for minority Nationalities and Peoples.
    3. Members of the House, on the basis of population and special representation of minority Nationalities and Peoples, shall not exceed 550; of these, minority Nationalities and Peoples shall have at least 20 seats. Particulars shall be determined by law.
    … (Art. 54)
  • Amharic

    2. የምክር ቤቱ አባላት በአንድ የምርጫ ክልል ውስጥ ከሌሎች ተወዳዳሪዎች መካከል አብላጫ ድምጽ ያገኘ ተወዳዳሪ አሸናፊ በሚሆንበት የምርጫ ሥርዓት ይመረጣሉ፡፡ የተለየ ውክልና ያሰፈልጋቸዋል ተብሎ የታመነባቸው አናሳ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በምርጫ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ይሆናሉ፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፡፡
    3. የምክር ቤቱ አባላት ቁጥር የሕዝብ ብዛትንና በልዩ ትኩረት ውክልና የሚሰጣቸው አናሳ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ቁጥር መሰረት በማድረግ 550 የማይበልጥ ሆኖ ከዚህ ውስጥ አናሳ ብሔረሰቦች 20 የማያንስ መቀመጫ ይኖራቸዋል፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይደነግጋል፡፡
    … (አንቀጽ 54)
Indigenous Peoples
  • English

    2. Each Nation, Nationality and People shall be represented in the House of the Federation by at least one member. Each Nation or Nationality shall be represented by one additional representative for each one million of its population.
    … (Art. 61)
  • Amharic

    2. እያንዳንዱ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ ቢያንስ አንድ ተወካይ ይኖረዋል፤በተጨማሪም የብሔር ወይም ብሔረሰቡ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ አንድ ተጨማሪ ወኪል ይኖረዋል፡፡
    … (አንቀጽ 61)
Limitations and/or Derogations
  • English

    2. Everyone has the right to the free development of his personality in a manner compatible with the rights of other citizens.
    … (Art. 24)
  • Amharic

    2. ማንኛውም ሰው የራሱን ስብዕና ከሌሎች ዜጐች መብቶች ጋር በተጣጣመ ሁኔታ በነጻ የማሳደግ መብት አለው፡፡
    … (አንቀጽ 24)
Limitations and/or Derogations
  • English

    4. a. When a state of emergency is declared, the Council of Ministers shall, in accordance with regulations it issues, have all necessary power to protect the country's peace and sovereignty, and to maintain public security, law and order.
    b. The Council of Ministers shall have the power to suspend such political and democratic rights contained in this Constitution to the extent necessary to avert the conditions that required the declaration of a state of emergency.
    c. In the exercise of its emergency powers the Council of Ministers cannot, however, suspend or limit the rights provided for in Articles 1, 18, 25, and sub-Articles 1 and 2 of Article 39 of this Constitution.
    5. The House of Peoples' Representatives, while declaring a state of emergency, shall simultaneously establish a State of Emergency Inquiry Board, comprising of seven persons to be chosen and assigned by the House from among its members and from legal experts.
    6. The State of Emergency Inquiry Board shall have the following powers and responsibilities:
    a. To make public within one month the names of all individuals arrested on account of the state of emergency together with the reasons for their arrest.
    b. To inspect and follow up that no measure taken during the state of emergency is inhumane.
    c. To recommend to the Prime Minister or to the Council of Ministers corrective measures if it finds any case of inhumane treatment.
    d. To ensure the prosecution of perpetrators of inhumane acts.
    e. To submit its views to the House of Peoples' Representatives on a request to extend the duration of the state of emergency. (Art. 93)
  • Amharic

    4. ሀ/ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሚታወጅበት ጊዜ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣቸው ደንቦች መሰረት የሀገርን ሰላምና ሕልውና፣ የሕዝብን ደህንነት፣ሕግና ሥርዓትን የማስከበር ሥልጣን ይኖረዋል፡፡
    ለ/ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሥልጣን በሕገ መንግሥቱ የተቀመጡትን መሰረታዊ የፖለቲካና የዴሞክራሲ መብቶችን፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማወጅ ምክንያት የሆነውን ጉዳይ ለማስወገድ ተፈላጊ ሆኖ በተገኘውደረጃ፣ እስከ ማገድ ሊደርስ የሚችል ነው፡፡
    ሐ/ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሥራ የሚያወጣቸው ድንጋጌዎችና የሚወስዳቸው እርምጃዎች በማናቸውም ረገድ በዚህ ሕገመንግሥት አንቀጽ 1፣፣ 18፣ 25፣ እና 39 ንዑስ አንቀጽ 1 እና 2 የተቀመጡትን መብቶች የሚገድቡ ሊሆኑ አይችሉም፡፡
    5. በሀገሪቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሚታወጅበት ወቅት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከአባላቱና ከሕግ ባለሙያዎች መርጦ የሚመድባቸው ሰባት አባላት ያሉት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ ያቋቁማል፡፡ ቦርዱ አዋጁ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚጸድቅበት ጊዜ ይቋቋማል፣
    6. የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ የሚከተሉት ሥልጣንና ኃላፊነቶች አሉት፡፡
    ሀ/ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት የታሰሩትን ግለሰቦች ስም በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይፋ ማድረግና የታሰሩበትን ምክንያት መግለጽ፣
    ለ/ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወቅት የሚወሰዱት እርምጃዎች በማናቸውም ረገድ ኢሰብዓዊ አለመሆናቸውን መቆጣጠርና መከታተል፣
    ሐ/ ማናቸውም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እርምጃ ኢሰብዓዊ መሆኑን ሲያምንበት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወይም የሚኒስሮች ምክር ቤት እርምጃውን እንዲያስተካክል ሐሳብ መስጠት፣
    መ/ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እርምጃዎች ኢሰብዓዊ ድርጊት የሚፈጽሙትን ሁሉ ለፍርድ እንዲቀርቡ ማድረግ፣
    ሠ/ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲቀጥል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄ ሲቀርብ ያለውን አስተያየት ለምክር ቤቱ ማቅረብ፡፡ (አንቀጽ 93)
Marriage and Family Life
  • English
    1. Men and women, without any distinction as to race, nation, nationality or religion, who have attained marriageable age as defined by law, have the right to marry and found a family. They have equal rights while entering into, during marriage and at the time of divorce. Laws shall be enacted to ensure the protection of rights and interests of children at the time of divorce.
    2. Marriage shall be entered into only with the free and full consent of the intending spouses.
    3. The family is the natural and fundamental unit of society and is entitled to protection by society and the State.
    4. In accordance with provisions to be specified by law, a law giving recognition to marriage concluded under systems of religious or customary laws may be enacted.
    5. This Constitution shall not preclude the adjudication of disputes relating to personal and family laws in accordance with religious or customary laws, with the consent of the parties to the dispute. Particulars shall be determined by law. (Art. 34)
  • Amharic
    1. በሕግ ከተወሰነው የጋብቻ ዕድሜ የደረሱ ወንዶችና ሴቶች በዘር፣ በብሔር፣በብሔረሰብ ወይም በሃይማኖት ልዩነት ሳይደረግባቸው የማግባትና ቤተሰብ የመመስረት መብት አላቸው፡፡ በጋብቻ አፈጻጸም፣ በጋብቻው ዘመንና በፍቺ ጊዜ እኩል መብት አላቸው፡፡ በፍቺም ጊዜ የልጆችን መብትና ጥቅም እንዲከበር የሚያደርጉ ድንጋጌዎች ይደነገጋሉ፡፡
    2. ጋብቻ በተጋቢዎች ነጻና ሙሉ ፈቃድ ላይ ብቻ ይመሰረታል፡፡
    3. ቤተሰብ የኅብረተሰብ የተፈጥሮ መሰረታዊ መነሻ ነው፡፡ ከኅብረተሰብና ከመንግሥት ጥበቃ የማግኘት መብት አለው፡፡
    4. በሕግ በተለይ በሚዘረዘረው መሰረት በሃይማኖት፣ በባሕል የሕግ ሥርዓቶች ላይ ተመስርትው ለሚፈጸሙ ጋብቻዎች እውቅና የሚሰጥ ሕግ ሊወጣ ይችላል፡፡
    5. ይህ ሕገ መንግሥት የግል እና የቤተሰብ ሕግን በተመለከተ በተከራካሪዎች ፈቃድ በሃይማኖቶች ወይም በባሕሎች ሕጐች መሰረት መዳኘትን አይከለክልም፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፡፡ (አንቀጽ 34)
Marriage and Family Life
  • English

    2. Women have equal rights with men in marriage as prescribed by this Constitution.

    5. a. Women have the right to maternity leave with full pay. The duration of maternity leave shall be determined by law taking into account the nature of the work, the health of the mother and the well-being of the child and family.
    b. Maternity leave may, in accordance with the provisions of law, include prenatal leave with full pay.

    9. To prevent harm arising from pregnancy and childbirth and in order to safeguard their health, women have the right of access to family planning education, information and capacity. (Art. 35)
  • Amharic

    2. ሴቶች በዚህ ሕገ መንግሥት በተደነገገው መሰረት በጋብቻ ከወንዶች ጋር እኩል መብት አላቸው፡፡

    5. ሀ/ ሴቶች የወሊድ ፈቃድ ከሙሉ የደመወዝ ክፍያ ጋር የማግኘት መብት አላቸው፡፡ የወሊድ ፈቃድ ርዝመት ሴቷ የምትሠራውን ሥራ ሁኔታ፣የሴቷን ጤንነት፣ የሕጻኑንና የቤተሰቡን ደህንነት ከግምት ውስጥ በማስገባት በሕግ ይወሰናል፡፡
    ለ/ የወሊድ ፈቃድ በሕግ በሚወሰነው መሰረት ከሙሉ የደመወዝ ክፍያ ጋር የሚሰጥ የእርግዝና ፈቃድን ሊጨምር ይችላል፡፡

    9. ሴቶች በእርግዝናና በወሊድ ምክንያት የሚደርስባቸውን ጉዳት ለመከላከልና ጤንነታቸውን ለማስጠበቅ የሚያስችል የቤተሰብ ምጣኔ ትምህርት፣ መረጃ እና አቅም የማግኘት መብት አላቸው፡፡ (አንቀጽ 35)
Marriage and Family Life
  • English
    1. Every child has the right:

    c. To know and be cared for by his or her parents or legal guardians;

    4. Children born out of wedlock shall have the same rights as children born of wedlock.
    … (Art. 36)
  • Amharic
    1. ማንኛውም ሕጻን የሚከተሉት መብቶች አሉት፤

    ሐ/ ወላጆቹን ወይም በሕግ የማሳደግ መብት ያላቸውን ሰዎች የማወቅና የእነሱንም እንክብካቤ የማግኘት፣

    4. ከጋብቻ ውጭ የተወለዱ ሕጻናት በጋብቻ ከተወለዱ ሕጻናት ጋር እኩል መብት አላቸው፡፡
    … (አንቀጽ 36)
Minorities
  • English

    2. Members of the House shall be elected from candidates in each electoral district by a plurality of the votes cast. Provisions shall be made by law for special representation for minority Nationalities and Peoples.
    3. Members of the House, on the basis of population and special representation of minority Nationalities and Peoples, shall not exceed 550; of these, minority Nationalities and Peoples shall have at least 20 seats. Particulars shall be determined by law.
    … (Art. 54)
  • Amharic

    2. የምክር ቤቱ አባላት በአንድ የምርጫ ክልል ውስጥ ከሌሎች ተወዳዳሪዎች መካከል አብላጫ ድምጽ ያገኘ ተወዳዳሪ አሸናፊ በሚሆንበት የምርጫ ሥርዓት ይመረጣሉ፡፡ የተለየ ውክልና ያሰፈልጋቸዋል ተብሎ የታመነባቸው አናሳ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በምርጫ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ይሆናሉ፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፡፡
    3. የምክር ቤቱ አባላት ቁጥር የሕዝብ ብዛትንና በልዩ ትኩረት ውክልና የሚሰጣቸው አናሳ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ቁጥር መሰረት በማድረግ 550 የማይበልጥ ሆኖ ከዚህ ውስጥ አናሳ ብሔረሰቦች 20 የማያንስ መቀመጫ ይኖራቸዋል፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይደነግጋል፡፡
    … (አንቀጽ 54)
Participation in Public Life and Institutions
  • English

    3. The historical legacy of inequality and discrimination suffered by women in Ethiopia taken into account, women, in order to remedy this legacy, are entitled to affirmative measures. The purpose of such measures shall be to provide special attention to women so as to enable them to compete and participate on the basis of equality with men in political, social and economic life as well as in public and private institutions.

    6. Women have the right to full consultation in the formulation of national development policies, the designing and execution of projects, and particularly in the case of projects affecting the interests of women.
    … (Art. 35)
  • Amharic

    3. ሴቶች በበታችነትና በልዩነት በመታየታቸው የደረሰባቸውን የታሪክ ቅርስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህ ቅርስ እንዲታረምላቸው በተጨማሪ የድጋፍ እርምጃዎች ተጠቃሚ የመሆን መብት አላቸው፡፡ በዚህ በኩል የሚወሰዱት እርምጃዎች ዓላማ በፖለቲካዊ፣ በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ መስኮች እንዲሁም በመንግሥት እና በግል ተቋሞች ውስጥ ሴቶች ከወንዶች ጋር በእኩልነት ተወዳዳሪና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ እንዲቻል ልዩ ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡

    6. ሴቶች በብሔራዊ የልማት ፖሊሲዎች ዕቅድና በኘሮጀክቶች ዝግጅትና አፈጻጸም፣በተለይ የሴቶችን ጥቅም በሚነኩ ኘሮጀክቶች ሐሳባቸውን በተሟላ ሁኔታ እንዲሰጡ የመጠየቅ መብት አላቸው፡፡
    … (አንቀጽ 35)
Participation in Public Life and Institutions
  • English
    1. Every Ethiopian national without any discrimination based on colour, race, nation, nationality, sex, language, religion, political or other opinion or other status, has the following rights:
    a. to take part in the conduct of public affairs, directly and through freely chosen representatives;
    … (Art. 38)
  • Amharic
    1. ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በቀለም፣ በዘር፣ በብሔር፣ በብሔረሰብ፣ በጾታ፣በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ ወይም በሌላ አመለከካከት ወይም በሌላ አቋም ላይ የተመሰረተ ልዩነት ሳይደረግበት የሚከተሉት መብቶች አሉት፤
    ሀ/ በቀጥታ እና በነጻነት በመረጣቸው ተወካዮች አማካኝነት በሕዝብ ጉዳይ አስተዳደር የመሳተፍ፣
    … (አንቀጽ 38)
Participation in Public Life and Institutions
  • English

    7. Government shall ensure the participation of women in equality with men in all economic and social development endeavors.
    … (Art. 89)
  • Amharic

    7. መንግሥት በሀገር ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ልማት እንቅስቃሴ ውስጥ ሴቶች ከወንዶች ጋር በእኩልነት የሚሳተፉበትን ሁኔታ የማመቻቸት ኃላፊነት አለበት፡፡
    … (አንቀጽ 89)
Political Rights and Association
  • English
    Every person has the right to freedom of association for any cause or purpose. … (Art. 31)
  • Amharic
    ማንኛውም ሰው ለማንኛውም ዓላማ በማኅበር የመደራጀት መብት አለው፡፡ … (አንቀጽ 31)
Political Rights and Association
  • English

    3. The historical legacy of inequality and discrimination suffered by women in Ethiopia taken into account, women, in order to remedy this legacy, are entitled to affirmative measures. The purpose of such measures shall be to provide special attention to women so as to enable them to compete and participate on the basis of equality with men in political, social and economic life as well as in public and private institutions.
    … (Art. 35)
  • Amharic

    3. ሴቶች በበታችነትና በልዩነት በመታየታቸው የደረሰባቸውን የታሪክ ቅርስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህ ቅርስ እንዲታረምላቸው በተጨማሪ የድጋፍ እርምጃዎች ተጠቃሚ የመሆን መብት አላቸው፡፡ በዚህ በኩል የሚወሰዱት እርምጃዎች ዓላማ በፖለቲካዊ፣ በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ መስኮች እንዲሁም በመንግሥት እና በግል ተቋሞች ውስጥ ሴቶች ከወንዶች ጋር በእኩልነት ተወዳዳሪና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ እንዲቻል ልዩ ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡
    … (አንቀጽ 35)
Political Rights and Association
  • English
    1. Every Ethiopian national, without any discrimination based on colour, race, nation, nationality, sex, language, religion, political or other opinion or other status, has the following rights:
    a. To take part in the conduct of public affairs, directly and through freely chosen representatives;
    b. On the attainment of 18 years of age, to vote in accordance with law;
    c. To vote and to be elected at periodic elections to any office at any level of government; elections shall be by universal and equal suffrage and shall be held by secret ballot, guaranteeing the free expression of the will of the electors.
    2. The right of everyone to be a member of his own will in a political organization, labour union, trade organization, or employers' or professional association shall be respected if he or she meets the special and general requirements stipulated by such organization.
    3. Elections to positions of responsibility within any of the organizations referred to under sub-Article 2 of this Article shall be conducted in a free and democratic manner.
    4. The provisions of sub-Articles 2 and 3 of this Article shall apply to civic organizations which significantly affect the public interest. (Art. 38)
  • Amharic
    1. ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በቀለም፣ በዘር፣ በብሔር፣ በብሔረሰብ፣ በጾታ፣በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ ወይም በሌላ አመለከካከት ወይም በሌላ አቋም ላይ የተመሰረተ ልዩነት ሳይደረግበት የሚከተሉት መብቶች አሉት፤
    ሀ/ በቀጥታ እና በነጻነት በመረጣቸው ተወካዮች አማካኝነት በሕዝብ ጉዳይ አስተዳደር የመሳተፍ፣
    ለ/ ዕድሜው 18 ዓመት ሲሞላ በሕግ መሰረት የመምረጥ ፣
    ሐ/ በማናቸውም የመንግሥት ደረጃ በየጊዜው በሚካሄድ ምርጫ የመምረጥና የመመረጥ፡፡ ምርጫው ሁሉ አቀፍ፣ በሁሉም እኩልነት ላይ የተመሰረተና በሚስጥር ድምጽ አሰጣጥ መራጩ ፈቃዱን በነጻነት የሚገልጽበት ዋስትና የሚሰጥ መሆን አለበት፡፡
    2. በፖለቲካ ድርጅቶች፣ በሠራተኞች፣ በንግድ፣ በአሠሪዎችና በሙያ ማኅበራት ለተሳትፎ ድርጅቱ የሚጠይቀውን ጠቅላላና ልዩ የአባልነት መስፈርት የሚያሟላ ማንኛውም ሰው በፍላጐቱ አባል የመሆን መብቱ የተከበረ መሆን አለበት፡፡
    3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 በተመለከቱት ድርጅቶች ውስጥ ለኃላፊነት ቦታዎች የሚካሄዱ ምርጫዎች ነጻና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ይፈጸማሉ፡፡
    4. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 እና 3 ድንጋጌዎች የሕዝብን ጥቅም ሰፋ ባለ ሁኔታ የሚነኩ እስከሆነ ድረስ በሕዝባዊ ድርጅቶች ላይ ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡ (አንቀጽ 38)
Electoral Bodies
  • English
    1. There shall be established a National Election Board independent of any influence, to conduct in an impartial manner free and fair election in Federal and State constituencies.
    … (Art. 102)
  • Amharic
    1. በፌዴራልና በክልል የምርጫ ክልሎች ነጻና ትክክለኛ ምርጫ በገለለተኝነት እንዲያካሂድ ከማንኛውም ተጽእኖ ነጻ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ይቋቋማል፡፡
    … (አንቀጽ 102)
Head of State
  • English
    The President of the Federal Democratic Republic of Ethiopia is the Head of State. (Art. 69)
  • Amharic
    ኘሬዚዳንቱ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ርዕሰ ብሔር ነው፡፡ (አንቀጽ 69)
Head of State
  • English
    1. The House of Peoples' Representatives shall nominate the candidate for President.
    2. The nominee shall be elected President if a joint session of the House of Peoples' Representatives and the House of the Federation approves his candidacy by a two-thirds majority vote.
    … (Art. 70)
  • Amharic
    1. ለኘሬዚዳንትነት እጩ የማቅረብ ሥልጣን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው፡፡
    2. የቀረበው እጩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና በፌዴሬሽኑ ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ በሁለት ሦስተኛ ድምጽ ከተደገፈ ኘሬዚዳንት ይሆናል፡፡
    … (አንቀጽ 70)
Government
  • English
    1. The highest executive powers of the Federal Government are vested in the Prime Minister and in the Council of Ministers.
    … (Art. 72)
  • Amharic
    1. የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ የአስፈጻሚነት ሥልጣን የተሰጠው ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ነው፡፡
    … (አንቀጽ 72)
Government
  • English
    1. The Prime Minister shall be elected from among members of the House of Peoples' Representatives.
    2. Power of Government shall be assumed by the political party or a coalition of political parties that constitutes a majority in the House of Peoples' Representatives. (Art. 73)
  • Amharic
    1. ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መካከል ይመረጣል፡፡
    2. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አብላጫ መቀመጫ ያገኘው የፖለቲካ ድርጅት ወይም ያገኙት የፖለቲካ ድርጅቶች የመንግሥት ሥልጣን ይረከባል/ይረከባሉ፡፡ (አንቀጽ 73)
Government
  • English

    2. The Prime Minister shall submit for approval to the House of Peoples' Representatives nominees for ministerial posts from among members of the two Houses or from among persons who are not members of either House and possess the required qualifications.
    … (Art. 74)
  • Amharic

    2. ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚኒስትሮች ምክር ቤት አባሎችን ከሁለቱ ምክር ቤቶች አባላት ወይም ለሥራው ብቃት ካላቸው ሌሎች ግለሰቦች መካከል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በእጩነት አቅርቦ ሹመታቸውን ያጸድቃል፡፡
    … (አንቀጽ 74)
Government
  • English
    1. The Council of Ministers comprises the Prime Minister, the Deputy Prime Minister, Ministers and other members as may be determined by law.
    … (Art. 76)
  • Amharic
    1. የሚኒስትሮች ምክር ቤት፤ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስተር፣ ሚኒስትሮችና በሕግ በሚወሰን መሰረት ሌሎች አባሎች የሚገኙበት ምክር ቤት ነው፡፡
    … (አንቀጽ 76)
Legislature
  • English
    There shall be two Federal Houses: The House of Peoples' Representatives and the House of the Federation. (Art. 53)
  • Amharic
    የፌዴራሉ መንግሥት ሁለት ምክር ቤቶች ይኖሩታል፤ እነዚህም የሕዝብተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ናቸው፡፡ (አንቀጽ 53)
Legislature
  • English
    1. Members of the House of Peoples' Representatives shall be elected by the People for a term of five years on the basis of universal suffrage and by direct, free and fair elections held by secret ballot.
    2. Members of the House shall be elected from candidates in each electoral district by a plurality of the votes cast. Provisions shall be made by law for special representation for minority Nationalities and Peoples.
    3. Members of the House, on the basis of population and special representation of minority Nationalities and Peoples, shall not exceed 550; of these, minority Nationalities and Peoples shall have at least 20 seats. Particulars shall be determined by law.
    … (Art. 54)
  • Amharic
    1. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፤ ሁሉ አቀፍ፣ ነጻ ፣ ቀጥተኛ፣ ትክክለኛ በሆነና ድምጽ በሚስጥር በሚሰጥበት ሥርዓት በየአምስት ዓመቱ በሕዝብ ይመረጣሉ፡፡
    2. የምክር ቤቱ አባላት በአንድ የምርጫ ክልል ውስጥ ከሌሎች ተወዳዳሪዎች መካከል አብላጫ ድምጽ ያገኘ ተወዳዳሪ አሸናፊ በሚሆንበት የምርጫ ሥርዓት ይመረጣሉ፡፡ የተለየ ውክልና ያሰፈልጋቸዋል ተብሎ የታመነባቸው አናሳ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በምርጫ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ይሆናሉ፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፡፡
    3. የምክር ቤቱ አባላት ቁጥር የሕዝብ ብዛትንና በልዩ ትኩረት ውክልና የሚሰጣቸው አናሳ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ቁጥር መሰረት በማድረግ 550 የማይበልጥ ሆኖ ከዚህ ውስጥ አናሳ ብሔረሰቦች 20 የማያንስ መቀመጫ ይኖራቸዋል፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይደነግጋል፡፡
    … (አንቀጽ 54)
Legislature
  • English
    1. The House of the Federation is composed of representatives of Nations, Nationalities and Peoples.
    2. Each Nation, Nationality and People shall be represented in the House of the Federation by at least one member. Each Nation or Nationality shall be represented by one additional representative for each one million of its population.
    3. Members of the House of the Federation shall be elected by the State Councils. The State Councils may themselves elect representatives to the House of the Federation, or they may hold elections to have the representatives elected by the people directly. (Art. 61)
  • Amharic
    1. የፌዴሬሽን ምክር ቤት በፌዴራሉ መንግሥት አባል ክልሎች የሚገኙ ብሔሮች፣ብሔረሰቦች፣ ሕዝቦች የሚልኩዋቸው አባላት የሚወከሉበት ምክር ቤት ነው፡፡
    2. እያንዳንዱ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ ቢያንስ አንድ ተወካይ ይኖረዋል፤በተጨማሪም የብሔር ወይም ብሔረሰቡ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ አንድ ተጨማሪ ወኪል ይኖረዋል፡፡
    3. የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት በክልል ምክር ቤቶች ይመረጣሉ፤ የክልል ምክር ቤቶች በራሳቸው ወይም በቀጥታ በሕዝብ እንዲመረጡ በማድረግ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል እንዲወከሉ ያደርጋሉ፡፡ (አንቀጽ 61)
Property, Inheritance and Land Tenure
  • English

    7. Women have the right to acquire, administer, control, use and transfer property. In particular, they have equal rights with men with respect to use, transfer, administration and control of land. They shall also enjoy equal treatment in the inheritance of property.
    … (Art. 35)
  • Amharic

    7. ሴቶች ንብረት የማፍራት፣ የማስተዳደር፣ የመቆጣጠር፣ የመጠቀምና የማስተላለፍ መብት አላቸው፡፡ በተለይም መሬትን በመጠቀም፣ በማስተላለፍ፣ በማስተዳደርና በመቆጣጠር ረገድ ከወንዶች ጋር እኩል መብት አላቸው፡፡ እንዲሁም ውርስን በሚመለከት በእኩልነት የመታየት መብት አላቸው፡፡
    … (አንቀጽ 35)
Property, Inheritance and Land Tenure
  • English
    1. Every Ethiopian citizen has the right to the ownership of private property. Unless prescribed otherwise by law on account of public interest, this right shall include the right to acquire, to use and, in a manner compatible with the rights of other citizens, to dispose of such property by sale or bequest or to transfer it otherwise.
    2. "Private property", for the purpose of this Article, shall mean any tangible or intangible product which has value and is produced by the labour, creativity, enterprise or capital of an individual citizen, associations which enjoy juridical personality under the law, or in appropriate circumstances, by communities specifically empowered by law to own property in common.
    3. The right to ownership of rural and urban land, as well as of all natural resources, is exclusively vested in the State and in the peoples of Ethiopia. Land is a common property of the Nations, Nationalities and Peoples of Ethiopia and shall not be subject to sale or to other means of exchange.
    4. Ethiopian peasants have right to obtain land without payment and the protection against eviction from their possession. The implementation of this provision shall be specified by law.
    5. Ethiopian pastoralists have the right to free land for grazing and cultivation as well as the right not to be displaced from their own lands. The implementation shall be specified by law.

    7. Every Ethiopian shall have the full right to the immovable property he builds and to the permanent improvements he brings about on the land by his labour or capital. This right shall include the right to alienate, to bequeath, and, where the right of use expires, to remove his property, transfer his title, or claim compensation for it. Particulars shall be determined by law.
    … (Art. 40)
  • Amharic
    1. ማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ የግል ንብረት ባለቤት መሆኑ/መሆኗ ይከበርለታል/ ይከበርላታል፡፡ ይህ መብት የሕዝብን ጥቅም ለመጠበቅ በሌላ ሁኔታ በሕግ እስካልተወሰነ ድረስ ንብረት የመያዝና በንብረት የመጠቀም ወይም የሌሎችን ዜጐች መብቶች እስካልተቃረነ ድረስ ንብረትን የመሸጥ የማውረስ ወይም በሌላ መንገድ የማስተላለፍ መብቶችን ያካትታል፡፡
    2. ለዚህ አንቀጽ ዓላማ «የግል ንብረት» ማለት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ወይም ሕጋዊ ሰውነት በሕግ የተሰጣቸው ኢትዮጵያዊ ማኅበራት ወይም አግባብ በአላቸው ሁኔታዎች በሕግ በተለየ በጋራ የንብረት ባለቤት እንዲሆኑ የተፈቀደላቸው ማኅበረሰቦች በጉልበታቸው፣ በመፍጠር ችሎታቸው ወይም በካፒታላቸው ያፈሩት ተጨባጭ የሆነና የተጨባጭነት ጠባይ ሳይኖረው ዋጋ ያለው ውጤት ነው፡፡
    3. የገጠርም ሆነ የከተማ መሬትና የተፈጥሮ ሀብት ባለቤትነት መብት የመንግሥትና የሕዝብ ብቻ ነው፡፡ መሬት የማይሸጥ የማይለወጥ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የጋራ ንብረት ነው፡፡
    4. የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች መሬት በነጻ የማግኘትና ከመሬታቸው ያለመነቀል መብታቸው የተከበረ ነው፡፡ አፈጻጸሙን በተመለከተ ዝርዝር ሕግ ይወጣል፡፡
    5. የኢትዮጵያ ዘላኖች ለግጦሽም ሆነ ለእርሻ የሚጠቀሙበት መሬት በነጻ የማግኘት፣የመጠቀምና ከመሬታቸው ያለመፈናቀል መብት አላቸው፡፡ ዝርዝር አፈጻጸሙ በሕግ ይወሰናል፡፡

    7. ማንም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ፣ ወይም በገንዘቡ በመሬት ላይ ለሚገነባው ቋሚ ንብረት ወይም ለሚያደርገው ቋሚ መሻሻል ሙሉ መብት አለው፡፡ ይህ መብት የመሸጥ፣ የመለወጥ፣ የማውረስ፣ የመሬት ተጠቃሚነቱ ሲቋረጥ ንብረቱን የማንሳት፣ ባለቤትነቱን የማዛወር ወይም የካሳ ክፍያ የመጠየቅ መብትን ያካትታል፡፡ ዝርዝር አፈጻጸሙ በሕግ ይወሰናል፡፡
    … (አንቀጽ 40)
Protection from Violence
  • English
    Every person has the inviolable and inalienable right to life, the security of person and liberty. (Art. 14)
  • Amharic
    ማንኛውም ሰው ሰብዓዊ በመሆኑ የማይደፈርና የማይገሰስ በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደህንነትና የነፃነት መብት አለው፡፡ (አንቀጽ 14)
Protection from Violence
  • English
    Everyone has the right to protection against bodily harm. (Art. 16)
  • Amharic
    ማንኛውም ሰው በአካሉ ላይ ጉዳት እንዳይደርስበት የመጠበቅ መብት አለው፡፡ (አንቀጽ 16)
Protection from Violence
  • English
    1. Everyone has the right to protection against cruel, inhuman or degrading treatment or punishment.
    2. No one shall be held in slavery or servitude. Trafficking in human beings for whatever purpose is prohibited.
    3. No one shall be required to perform forced or compulsory labour.
    … (Art. 18)
  • Amharic
    1. ማንኛውም ሰው ጭካኔ ከተሞላበት፣ ኢሰብዓዊ ከሆነ ወይም ክብሩን ከሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት የመጠበቅ መብት አለው፡፡
    2. ማንኛውም ሰው በባርነት ወይም በግዴታ አገልጋይነት ሊያዝ አይችልም፡፡ለማንኛውም ዓላማ በሰው የመነገድ ተግባር የተከለከለ ነው፡፡
    3. ማንኛውም ሰው በኃይል ተገዶ ወይም ግዴታ ለማሟላት ማንኛውንም ሥራ እንዲሠራ ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
    … (አንቀጽ 18)
Protection from Violence
  • English

    4. The State shall enforce the right of women to eliminate the influences of harmful customs. Laws, customs and practices that oppress or cause bodily or mental harm to women are prohibited.
    … (Art. 35)
  • Amharic

    4. ሴቶች ከጐጂ ባሕል ተጽዕኖ የመላቀቅ መብታቸውን መንግሥት ማስከበር አለበት፡፡ ሴቶችን የሚጨቁኑ ወይም በአካላቸው ወይም በአዕምሮአቸው ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ሕጐች፣ ወጐችና ልማዶች የተከለከሉ ናቸው፡፡
    … (አንቀጽ 35)
Protection from Violence
  • English
    1. Every child has the right:

    d. Not to be subject to exploitative practices, neither to be required nor permitted to perform work which may be hazardous or harmful to his or her education, health or wellbeing;
    e. To be free of corporal punishment or cruel and inhumane treatment in schools and other institutions responsible for the care of children.
    … (Art. 36)
  • Amharic
    1. ማንኛውም ሕጻን የሚከተሉት መብቶች አሉት፤

    መ/ ጉልበቱን ከሚበዘብዙ ልማዶች የመጠበቅ፣ በትምህርቱ፣ በጤናውና በደህንነቱ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ሥራዎች እንዲሠራ ያለመገደድ ወይም ከመሥራት የመጠበቅ፣
    ሠ/ በትምህርት ቤቶች ወይም በሕጻናት ማሳደጊያ ተቋሞች ውስጥ በአካሉ ከሚፈጸም ወይም ከጭካኔና ኢሰብዓዊ ከሆነ ቅጣት ነጻ የመሆን፡፡
    … (አንቀጽ 36)
Public Institutions and Services
  • English

    3. The family is the natural and fundamental unit of society and is entitled to protection by society and the State.
    … (Art. 34)
  • Amharic

    3. ቤተሰብ የኅብረተሰብ የተፈጥሮ መሰረታዊ መነሻ ነው፡፡ ከኅብረተሰብና ከመንግሥት ጥበቃ የማግኘት መብት አለው፡፡
    … (አንቀጽ 34)
Public Institutions and Services
  • English

    3. Every Ethiopian national has the right to equal access to publicly funded social services.
    4. The State has the obligation to allocate ever increasing resources to provide to the public health, education and other social services.
    … (Art. 41)
  • Amharic

    3. የኢትዮጵያ ዜጐች ሁሉ በመንግሥት ገንዘብ በሚካሄዱ ማኅበራዊ አገልግሎቶች በእኩልነት የመጠቀም መብት አላቸው፡፡
    4. መንግሥት የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች የማኅበራዊ አገልግሎቶችን ለሕዝብ ለማቅረብ በየጊዜው እየጨመረ የሚሄድ ሀብት ይመድባል፡፡
    … (አንቀጽ 41)
Public Institutions and Services
  • English

    2. Government has the duty to ensure that all Ethiopians get equal opportunity to improve their economic condition and to promote equitable distribution of wealth among them.
    … (Art. 89)
  • Amharic

    2. መንግሥት የኢትዮጵያውያንን የኢኮኖሚ ሁኔታዎች ለማሻሻል እኩል ዕድል እንዲኖራቸው ለማድረግና ሀብት ፍትሐዊ በሆነ መንገድ የሚከፋፈሉበትን ሁኔታ የማመቻቸት ግዴታ አለበት፡፡
    … (አንቀጽ 89)
Public Institutions and Services
  • English
    1. To the extent the country's resources permit, policies shall aim to provide all Ethiopians access to public health and education, clean water, housing, food and social security.
    … (Art. 90)
  • Amharic
    1. የሀየሀገሪቱ አቅም በፈቀደ መጠን ሁሉም ኢትዮጵያዊ የትምህርት፣ የጤና አገልግሎት፣ የንoህ ውሃ፣ የመኖሪያ፣ የምግብና የማኅበራዊ ዋስትና እንዲኖረው ይደረጋል፡፡
    … (አንቀጽ 90)
Sexual and Reproductive Rights
  • English

    9. To prevent harm arising from pregnancy and childbirth and in order to safeguard their health, women have the right of access to family planning education, information and capacity. (Art. 35)
  • Amharic

    9. ሴቶች በእርግዝናና በወሊድ ምክንያት የሚደርስባቸውን ጉዳት ለመከላከልና ጤንነታቸውን ለማስጠበቅ የሚያስችል የቤተሰብ ምጣኔ ትምህርት፣ መረጃ እና አቅም የማግኘት መብት አላቸው፡፡ (አንቀጽ 35)
Status of the Constitution
  • English
    We, the Nations, Nationalities and Peoples of Ethiopia: …
    Have therefore adopted, on 8 December 1994 this Constitution through representatives we have duly elected for this purpose as an instrument that binds us in a mutual commitment to fulfill the objectives and the principles set forth above. (Preamble)
  • Amharic
    እኛ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ …
    ይህ ሕገ መንግሥት ከዚህ በላይ ለገለጽናቸው ዓላማዎችና እምነቶች ማሰሪያ እንዲሆነንእንዲወክሉን መርጠን በላክናቸው ተወካዮቻቸን አማካይነት በሕገ መንግሥት ጉባኤ ዛሬ ኅዳር 29 ቀን 1987 አጽድቀነዋል፡፡ (መግቢያ)
Status of the Constitution
  • English
    1. The Constitution is the supreme law of the land. Any law, customary practice or a decision of an organ of state or a public official which contravenes this Constitution shall be of no effect.
    2. All citizens, organs of state, political organizations, other associations as well as their officials have the duty to ensure observance of the Constitution and to obey it.
    3. It is prohibited to assume state power in any manner other than that provided under the Constitution.
    … (Art. 9)
  • Amharic
    1. ሕገ መንግሥቱ የሀገሪቱ የበላይ ሕግ ነው፡፡ ማንኛውም ሕግ፣ ልማዳዊ አሰራር፣እንዲሁም የመንግሥት አካል ወይም ባለሥልጣን ውሳኔ ከዚህ ሕገ መንግሥት ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈጻሚነት አይኖረውም፡፡
    2. ማንኛውም ዜጋ፣ የመንግሥት አካላት፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ሌሎች ማኅበራት እንዲሁም ባለሥልጣኖቻቸው፣ ሕገ መንግሥቱን የማስከበርና ለሕገ መንግሥቱ ተገዢ የመሆን ኃላፊነት አለባቸው፡፡
    3. በዚህ ሕገ መንግሥት ከተደነገገው ውጭ በማናቸውም አኳኊን የመንግሥት ሥልጣን መያዝ የተከለከለ ነው፡፡
    … (አንቀጽ 9)
Status of International Law
  • English

    4. All international agreements ratified by Ethiopia are an integral part of the law of the land. (Art. 9)
  • Amharic

    4. ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች የሀገሪቱ ሕግ አካል ናቸው፡፡ (አንቀጽ 9)
Status of International Law
  • English

    2. The fundamental rights and freedoms specified in this Chapter5 shall be interpreted in a manner conforming to the principles of the Universal Declaration of Human Rights, International Covenants on Human Rights and International instruments adopted by Ethiopia. (Art. 13)
  • Amharic

    2. በዚህ ምዕራፍ የተዘረዘሩት መሠረታዊ የመብቶችና የነጻነቶች ድንጋጌዎች ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕግጋት፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ስምምነቶችና ዓለም አቀፍ ሰነዶች መርሆዎች ጋር በተጣጣመ መንገድ ይተረጐማል፡፡ (አንቀጽ 13)
Religious Law
  • English
    1. State and religion are separate.
    2. There shall be no state religion.
    3. The state shall not interfere in religious matters and religion shall not interfere in state affairs. (Art. 11)
  • Amharic
    1. መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው፡፡
    2. መንግሥታዊ ሃይማኖት አይኖርም፡፡
    3. መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፡፡ ሃይማኖትም በመንግሥት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፡፡ (አንቀጽ 11)
Religious Law
  • English

    4. In accordance with provisions to be specified by law, a law giving recognition to marriage concluded under systems of religious or customary laws may be enacted.
    5. This Constitution shall not preclude the adjudication of disputes relating to personal and family laws in accordance with religious or customary laws, with the consent of the parties to the dispute. Particulars shall be determined by law. (Art. 34)
  • Amharic

    4. በሕግ በተለይ በሚዘረዘረው መሰረት በሃይማኖት፣ በባሕል የሕግ ሥርዓቶች ላይ ተመስርትው ለሚፈጸሙ ጋብቻዎች እውቅና የሚሰጥ ሕግ ሊወጣ ይችላል፡፡
    5. ይህ ሕገ መንግሥት የግል እና የቤተሰብ ሕግን በተመለከተ በተከራካሪዎች ፈቃድ በሃይማኖቶች ወይም በባሕሎች ሕጐች መሰረት መዳኘትን አይከለክልም፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፡፡ (አንቀጽ 34)
Religious Law
  • English

    5. Pursuant to sub-Article 5 of Article 34 the House of Peoples’ Representatives and State Councils can establish or give official recognition to religious and customary courts. Religious and customary courts that had state recognition and functioned prior to the adoption of the Constitution shall be organized on the basis of recognition accorded to them by this Constitution. (Art. 78)
  • Amharic

    5. የህዝብ ተወካዬች ምክር ቤትና የክልል ምክር ቤቶች በኣንቀጽ 34 ንኡስ ኣንቀጽ 5 መሰረት የሃማኖትና የባሕል ፍርድ ቤቶችን ሊያቋቁሙ ወይም እውቅና ሊሰጡ ይችላሉ፡፡ ይህ ሕገ መንግሥት ከመጽደቁ በፊት በመንግሥት እውቅና አግኝተው ሲሰራባቸው የነበሩ የሃይማኖቶችና የባሕል ፍርድ ቤቶች በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት እውቅና አግኝተው ይደራጃሉ፡፡ (አንቀጽ 78)
Customary Law
  • English
    1. The Constitution is the supreme law of the land. Any law, customary practice or a decision of an organ of state or a public official which contravenes this Constitution shall be of no effect.
    … (Art. 9)
  • Amharic
    1. ሕገ መንግሥቱ የሀገሪቱ የበላይ ሕግ ነው፡፡ ማንኛውም ሕግ፣ ልማዳዊ አሰራር፣እንዲሁም የመንግሥት አካል ወይም ባለሥልጣን ውሳኔ ከዚህ ሕገ መንግሥት ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈጻሚነት አይኖረውም፡፡
    … (አንቀጽ 9)
Customary Law
  • English

    4. In accordance with provisions to be specified by law, a law giving recognition to marriage concluded under systems of religious or customary laws may be enacted.
    5. This Constitution shall not preclude the adjudication of disputes relating to personal and family laws in accordance with religious or customary laws, with the consent of the parties to the dispute. Particulars shall be determined by law. (Art. 34)
  • Amharic

    4. በሕግ በተለይ በሚዘረዘረው መሰረት በሃይማኖት፣ በባሕል የሕግ ሥርዓቶች ላይ ተመስርትው ለሚፈጸሙ ጋብቻዎች እውቅና የሚሰጥ ሕግ ሊወጣ ይችላል፡፡
    5. ይህ ሕገ መንግሥት የግል እና የቤተሰብ ሕግን በተመለከተ በተከራካሪዎች ፈቃድ በሃይማኖቶች ወይም በባሕሎች ሕጐች መሰረት መዳኘትን አይከለክልም፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፡፡ (አንቀጽ 34)
Customary Law
  • English

    4. The State shall enforce the right of women to eliminate the influences of harmful customs. Laws, customs and practices that oppress or cause bodily or mental harm to women are prohibited.
    … (Art. 35)
  • Amharic

    4. ሴቶች ከጐጂ ባሕል ተጽዕኖ የመላቀቅ መብታቸውን መንግሥት ማስከበር አለበት፡፡ ሴቶችን የሚጨቁኑ ወይም በአካላቸው ወይም በአዕምሮአቸው ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ሕጐች፣ ወጐችና ልማዶች የተከለከሉ ናቸው፡፡
    … (አንቀጽ 35)
Customary Law
  • English

    5. Pursuant to sub-Article 5 of Article 34 the House of Peoples’ Representatives and State Councils can establish or give official recognition to religious and customary courts. Religious and customary courts that had state recognition and functioned prior to the adoption of the Constitution shall be organized on the basis of recognition accorded to them by this Constitution. (Art. 78)
  • Amharic

    5. የህዝብ ተወካዬች ምክር ቤትና የክልል ምክር ቤቶች በኣንቀጽ 34 ንኡስ ኣንቀጽ 5 መሰረት የሃማኖትና የባሕል ፍርድ ቤቶችን ሊያቋቁሙ ወይም እውቅና ሊሰጡ ይችላሉ፡፡ ይህ ሕገ መንግሥት ከመጽደቁ በፊት በመንግሥት እውቅና አግኝተው ሲሰራባቸው የነበሩ የሃይማኖቶችና የባሕል ፍርድ ቤቶች በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት እውቅና አግኝተው ይደራጃሉ፡፡ (አንቀጽ 78)
Customary Law
  • English
    1. Government shall have the duty to support, on the basis of equality, the growth and enrichment of cultures and traditions that are compatible with fundamental rights, human dignity, democratic norms and ideals, and the provisions Constitution.
    … (Art. 91)
  • Amharic
    1. መንግሥት መሰረታዊ መብቶችንና ሰብዓዊ ክብርን፣ ዴሞክራሲንና ሕገ መንግሥቱን የማይቃረኑ ባሕሎችና ልማዶች በእኩልነት እንዲጐለብቱና እንዲያድጉ የመርዳት ኃላፊነት አለበት፡፡
    … (አንቀጽ 91)
Women’s Rights
  • English
    1. Women shall, in the enjoyment of rights and protections provided for by this Constitution, have equal right with men.
    2. Women have equal rights with men in marriage as prescribed by this Constitution.
    3. The historical legacy of inequality and discrimination suffered by women in Ethiopia taken into account, women, in order to remedy this legacy, are entitled to affirmative measures. The purpose of such measures shall be to provide special attention to women so as to enable them to compete and participate on the basis of equality with men in political, social and economic life as well as in public and private institutions.
    4. The State shall enforce the right of women to eliminate the influences of harmful customs. Laws, customs and practices that oppress or cause bodily or mental harm to women are prohibited.
    5. a. Women have the right to maternity leave with full pay. The duration of maternity leave shall be determined by law taking into account the nature of the work, the health of the mother and the well-being of the child and family.
    b. Maternity leave may, in accordance with the provisions of law, include prenatal leave with full pay.
    6. Women have the right to full consultation in the formulation of national development policies, the designing and execution of projects, and particularly in the case of projects affecting the interests of women.
    7. Women have the right to acquire, administer, control, use and transfer property. In particular, they have equal rights with men with respect to use, transfer, administration and control of land. They shall also enjoy equal treatment in the inheritance of property.
    8. Women shall have a right to equality in employment, promotion, pay, and the transfer of pension entitlements.
    9. To prevent harm arising from pregnancy and childbirth and in order to safeguard their health, women have the right of access to family planning education, information and capacity. (Art. 35)
  • Amharic
    1. ሴቶች ይህ ሕገ መንግሥት በአረጋገጣቸው መብቶችና ጥበቃዎች በመጠቀም ረገድ ከወንዶች ጋር እኩል መብት አላቸው፡፡
    2. ሴቶች በዚህ ሕገ መንግሥት በተደነገገው መሰረት በጋብቻ ከወንዶች ጋር እኩል መብት አላቸው፡፡
    3. ሴቶች በበታችነትና በልዩነት በመታየታቸው የደረሰባቸውን የታሪክ ቅርስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህ ቅርስ እንዲታረምላቸው በተጨማሪ የድጋፍ እርምጃዎች ተጠቃሚ የመሆን መብት አላቸው፡፡ በዚህ በኩል የሚወሰዱት እርምጃዎች ዓላማ በፖለቲካዊ፣ በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ መስኮች እንዲሁም በመንግሥት እና በግል ተቋሞች ውስጥ ሴቶች ከወንዶች ጋር በእኩልነት ተወዳዳሪና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ እንዲቻል ልዩ ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡
    4. ሴቶች ከጐጂ ባሕል ተጽዕኖ የመላቀቅ መብታቸውን መንግሥት ማስከበር አለበት፡፡ ሴቶችን የሚጨቁኑ ወይም በአካላቸው ወይም በአዕምሮአቸው ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ሕጐች፣ ወጐችና ልማዶች የተከለከሉ ናቸው፡፡
    5. ሀ/ ሴቶች የወሊድ ፈቃድ ከሙሉ የደመወዝ ክፍያ ጋር የማግኘት መብት አላቸው፡፡ የወሊድ ፈቃድ ርዝመት ሴቷ የምትሠራውን ሥራ ሁኔታ፣የሴቷን ጤንነት፣ የሕጻኑንና የቤተሰቡን ደህንነት ከግምት ውስጥ በማስገባት በሕግ ይወሰናል፡፡
    ለ/ የወሊድ ፈቃድ በሕግ በሚወሰነው መሰረት ከሙሉ የደመወዝ ክፍያ ጋር የሚሰጥ የእርግዝና ፈቃድን ሊጨምር ይችላል፡፡
    6. ሴቶች በብሔራዊ የልማት ፖሊሲዎች ዕቅድና በኘሮጀክቶች ዝግጅትና አፈጻጸም፣በተለይ የሴቶችን ጥቅም በሚነኩ ኘሮጀክቶች ሐሳባቸውን በተሟላ ሁኔታ እንዲሰጡ የመጠየቅ መብት አላቸው፡፡
    7. ሴቶች ንብረት የማፍራት፣ የማስተዳደር፣ የመቆጣጠር፣ የመጠቀምና የማስተላለፍ መብት አላቸው፡፡ በተለይም መሬትን በመጠቀም፣ በማስተላለፍ፣ በማስተዳደርና በመቆጣጠር ረገድ ከወንዶች ጋር እኩል መብት አላቸው፡፡ እንዲሁም ውርስን በሚመለከት በእኩልነት የመታየት መብት አላቸው፡፡
    8. ሴቶች የቅጥር፣ የሥራ እድገት፣ የእኩል ክፍያና ጡረታን የማስተላለፍ እኩል መብት አላቸው፡፡
    9. ሴቶች በእርግዝናና በወሊድ ምክንያት የሚደርስባቸውን ጉዳት ለመከላከልና ጤንነታቸውን ለማስጠበቅ የሚያስችል የቤተሰብ ምጣኔ ትምህርት፣ መረጃ እና አቅም የማግኘት መብት አላቸው፡፡ (አንቀጽ 35)
1

Constitution of the Federal Democratic Republic of Ethiopia 1994 (English). According to Art. 106: “The Amharic version of this Constitution shall have final legal authority.” There are discrepancies in the content of the English and Amharic texts.

2

Constitution of the Federal Democratic Republic of Ethiopia 1994 (Amharic). Copy obtained from the Ministry of Justice, Ethiopia.

Links to all sites last visited 6 March 2024
3
Chapter Three on Fundamental Rights and Freedoms.
4
Chapter Three on Fundamental Rights and Freedoms.
5
Chapter Three on Fundamental Rights and Freedoms.