- English
1. State and religion are separate.
2. There shall be no state religion.
3. The state shall not interfere in religious matters and religion shall not interfere in state affairs. (Art. 11) - Amharic
1. መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው፡፡
2. መንግሥታዊ ሃይማኖት አይኖርም፡፡
3. መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፡፡ ሃይማኖትም በመንግሥት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፡፡ (አንቀጽ 11)
- English
…
4. In accordance with provisions to be specified by law, a law giving recognition to marriage concluded under systems of religious or customary laws may be enacted.
5. This Constitution shall not preclude the adjudication of disputes relating to personal and family laws in accordance with religious or customary laws, with the consent of the parties to the dispute. Particulars shall be determined by law. (Art. 34) - Amharic
…
4. በሕግ በተለይ በሚዘረዘረው መሰረት በሃይማኖት፣ በባሕል የሕግ ሥርዓቶች ላይ ተመስርትው ለሚፈጸሙ ጋብቻዎች እውቅና የሚሰጥ ሕግ ሊወጣ ይችላል፡፡
5. ይህ ሕገ መንግሥት የግል እና የቤተሰብ ሕግን በተመለከተ በተከራካሪዎች ፈቃድ በሃይማኖቶች ወይም በባሕሎች ሕጐች መሰረት መዳኘትን አይከለክልም፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፡፡ (አንቀጽ 34)
- English
…
5. Pursuant to sub-Article 5 of Article 34 the House of Peoples’ Representatives and State Councils can establish or give official recognition to religious and customary courts. Religious and customary courts that had state recognition and functioned prior to the adoption of the Constitution shall be organized on the basis of recognition accorded to them by this Constitution. (Art. 78) - Amharic
…
5. የህዝብ ተወካዬች ምክር ቤትና የክልል ምክር ቤቶች በኣንቀጽ 34 ንኡስ ኣንቀጽ 5 መሰረት የሃማኖትና የባሕል ፍርድ ቤቶችን ሊያቋቁሙ ወይም እውቅና ሊሰጡ ይችላሉ፡፡ ይህ ሕገ መንግሥት ከመጽደቁ በፊት በመንግሥት እውቅና አግኝተው ሲሰራባቸው የነበሩ የሃይማኖቶችና የባሕል ፍርድ ቤቶች በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት እውቅና አግኝተው ይደራጃሉ፡፡ (አንቀጽ 78)
- English
1. The Constitution is the supreme law of the land. Any law, customary practice or a decision of an organ of state or a public official which contravenes this Constitution shall be of no effect.
… (Art. 9) - Amharic
1. ሕገ መንግሥቱ የሀገሪቱ የበላይ ሕግ ነው፡፡ ማንኛውም ሕግ፣ ልማዳዊ አሰራር፣እንዲሁም የመንግሥት አካል ወይም ባለሥልጣን ውሳኔ ከዚህ ሕገ መንግሥት ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈጻሚነት አይኖረውም፡፡
… (አንቀጽ 9)
- English
…
4. In accordance with provisions to be specified by law, a law giving recognition to marriage concluded under systems of religious or customary laws may be enacted.
5. This Constitution shall not preclude the adjudication of disputes relating to personal and family laws in accordance with religious or customary laws, with the consent of the parties to the dispute. Particulars shall be determined by law. (Art. 34) - Amharic
…
4. በሕግ በተለይ በሚዘረዘረው መሰረት በሃይማኖት፣ በባሕል የሕግ ሥርዓቶች ላይ ተመስርትው ለሚፈጸሙ ጋብቻዎች እውቅና የሚሰጥ ሕግ ሊወጣ ይችላል፡፡
5. ይህ ሕገ መንግሥት የግል እና የቤተሰብ ሕግን በተመለከተ በተከራካሪዎች ፈቃድ በሃይማኖቶች ወይም በባሕሎች ሕጐች መሰረት መዳኘትን አይከለክልም፡፡ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፡፡ (አንቀጽ 34)
- English
…
4. The State shall enforce the right of women to eliminate the influences of harmful customs. Laws, customs and practices that oppress or cause bodily or mental harm to women are prohibited.
… (Art. 35) - Amharic
…
4. ሴቶች ከጐጂ ባሕል ተጽዕኖ የመላቀቅ መብታቸውን መንግሥት ማስከበር አለበት፡፡ ሴቶችን የሚጨቁኑ ወይም በአካላቸው ወይም በአዕምሮአቸው ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ሕጐች፣ ወጐችና ልማዶች የተከለከሉ ናቸው፡፡
… (አንቀጽ 35)
- English
…
5. Pursuant to sub-Article 5 of Article 34 the House of Peoples’ Representatives and State Councils can establish or give official recognition to religious and customary courts. Religious and customary courts that had state recognition and functioned prior to the adoption of the Constitution shall be organized on the basis of recognition accorded to them by this Constitution. (Art. 78) - Amharic
…
5. የህዝብ ተወካዬች ምክር ቤትና የክልል ምክር ቤቶች በኣንቀጽ 34 ንኡስ ኣንቀጽ 5 መሰረት የሃማኖትና የባሕል ፍርድ ቤቶችን ሊያቋቁሙ ወይም እውቅና ሊሰጡ ይችላሉ፡፡ ይህ ሕገ መንግሥት ከመጽደቁ በፊት በመንግሥት እውቅና አግኝተው ሲሰራባቸው የነበሩ የሃይማኖቶችና የባሕል ፍርድ ቤቶች በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት እውቅና አግኝተው ይደራጃሉ፡፡ (አንቀጽ 78)
- English
1. Government shall have the duty to support, on the basis of equality, the growth and enrichment of cultures and traditions that are compatible with fundamental rights, human dignity, democratic norms and ideals, and the provisions Constitution.
… (Art. 91) - Amharic
1. መንግሥት መሰረታዊ መብቶችንና ሰብዓዊ ክብርን፣ ዴሞክራሲንና ሕገ መንግሥቱን የማይቃረኑ ባሕሎችና ልማዶች በእኩልነት እንዲጐለብቱና እንዲያድጉ የመርዳት ኃላፊነት አለበት፡፡
… (አንቀጽ 91)
Constitution of the Federal Democratic Republic of Ethiopia 1995 (English). According to Art. 106: “The Amharic version of this Constitution shall have final legal authority.”
Chapter Three on Fundamental Rights and Freedoms.
Chapter Three on Fundamental Rights and Freedoms.
Chapter Three on Fundamental Rights and Freedoms.